
ለዝህ ጽሁፍ ያነሳሳኝ ፕሮፌሰር መረራ በፓርቲዎች ውይይት ጥቁሮች ወደ ነጮች ዩንቨርስቲ ኣልስስገባ ስላለው የአሜሪካ ኦክላሃማ እምትባል ክፍለሃገር አስተዳዳሪ ጥቁሮችን አናስገባም ብሎ ለፖሊሱ ሲያዘው ፕሬዝደንቱ ይደውልና ስልኩን ለፖሊስ ኣዛዡ ኣቀብለው ይለዋል ፕሬዝዳንቱም "ከአሁን በሁዋላ እማዝህ እኔ የአሜሪካን ፕሬዝደንት ነኝ እንጂ የክፍለሃገሩ ገዢ state governor አይደለም ጥቁሮቹን ወደ ዩንቨርስቲው አስገባቸው " ሲለው የፖሊስ አዛዡም yes sir ብሎ የፕሬዝደንቱን ትእዛዝ ተቀብሎ ጥቁሮቹ ወደ ዩንቨርስቲው ቅጥር ገብተው እንዲማሩ አድርጎአል። rendition vs extradition.፦ ሲሆን በክልሎች መሃከል ወንጅለኛን በምን መልኩ ነው እሚለዋወጡት ? የፌደራል አቃቤ ህግና የፌደራል ፖሊስ ባንድ ሃገር ውስጥ ሌላ ክልል ውስጥ ሄዶ የሽሽን ወንጀለኛ በምን መልኩ ነው ይዘው ለፍርድ እሚያቀርቡት ? ይህ ተቁዋማዊ ዝርፊያ ሲፈጸም ኢህዴግ እንደ ድርጅት የት ነበረ ? አቶ ህይልማርያምም አቅቶአቸው ነበረ አሉ። ለሜቴክ የመርከቡን ጉዳይ አስተካክል ብለው ትእዛዝ ሲሰጡ የሰማቸው ኣልነበረም። ዶ/ ር አብይ ሜቴክ ለሁለት እንዲከፈል ሲያዙ በሙስና የሚጠረጠሩትን አንስተዋል ወ/ሮ አዜብ መስፍንን ግን የቦርድ አባል አድርገው ሾሙ ልማዘናጋት ሊሆን ይችላል ይህ ሹመት። ሌላው ደግሞ ባንቀፅ 28 መሰረት በሰብአዊ መብት ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች በይርጋ አይታገዱም። crimes againest humanity ሲሆኑ ይህም Gross Human Rights Violations ናቸው። ወንጀሉ ዓለም ዓቀፍ ባህሪ ያለው ሲሆን ይቅርታም ሆነ ምህረት አይደረግለትም ፥ ርእሰ ብሄሩም ቢሆን ምናልባት ወንጀለኛው ሞት ቢፈረድበት ወደ እድሜ ልክ ዝቅ ያደርጉለታል እንጂ ምህረትም ሆነ ይቅርታ አይደረግለትም። የፌደራሉ መንግስት ሙሰኞቹና በሰብአዊ መብት ጥሰት እሚጠየቁት ይሰጡኝ ሢል ለትግራይ ክልል ጥያቄን አቅርቦአል። በክልሎች መሃል በወንጀል እሚፈለግን ሰው ተላልፎ ስለመስጠት rendition /extradition በህግ የተቀመጠ ነገር ባይኖርም ፌልደራል ፖሊስና ጠቅላይ አቃቤ ህግ የስልጣን ወሰናቸው ያገሪቱ ግዛት መሆኑ የታወቀ ስለሆነ ክልሎች ይዘው ወንጀለኞችን የማስረከብ ግዴታ አለባቸው ፤ ማስጠጋትም ሆነ መሸሸግ የለባቸውም። ፌደራል ፖሊስም በየትኛውም የሃገሪቱ ክልል ተንቀሳቅሶ የሚፈልጋቸውን ሰዎች ይዞ ለፍርድ የማቅረብ ስልጣንና መብት አለው። በክልሎችባ በፌደራል መንግስት መሃከል በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎች ቅብብል ወይም አስተላልፎ ስለመስጠት extradition ምን እንደሚመስል በህግ የተነገገ ነገር ወይም ህገ መንግስቱ ምንም አይልም ። ፕሮፌሰር መረራ እንዳሉት እንደ ኦክላሃማ ፖሊስ yes sir ብሎ እሚታዘዝ ያስፈልጋል።Todos os Direitos Reservados